የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እየተካሄደ በሚገኝው የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት

👉 17 ሚሊየን ሊትር ወተት፤8 ሚሊየን 815 ሺ እንቁላል፤636 ቶን የስጋ ምርት 26.17 ቶን የማር ምርት ተመርቷል፣

👉 አንድ ሺ 130 ኩንታል የቡና ሰብል ማምረት ተችሏል፣

👉በሌማት ትሩፋት 3 የወተት፤4 የእንቁላል፤3 የአሳና 2 የማር መንደሮችን መፍጠር ተችሏል፣

👉 በበጋ መስኖ የአትክልትና የሥራሥር ምርት በሁለት ዙር 2 ሺ 953 ሄክታር ማልማት ተችሏል፣

👉 30ሺ 612 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ኮምፖስት ማቅረብ ተችሏል።

👉 ለበጋ መስኖ ልማት 650 ኩንታል ምርጥ ዘር፣ 33 የውኃ መሳቢያ ሞተሮች ተሰራጭቷል፣

👉 አንድ ሺ 800 አርሶ አደሮችንም የሰብል መውቂያ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፣

👉 በግሉ ዘርፍ 39ሺ 450 የዶሮ ጫጩቶችን ለማሰራጨት ተችሏል።

👉 የአሳ ጫጩት ስርጭትን በተመለከተም 16 ሺ150 ጫጬቶችን ማሰራጨት ተችሏል፣

👉 በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል

👉 በክልሉ መንግስት በጀት ከ38 ሺ በላይ ተማሪዎችን ያቀፈ የትምህርት ቤት ምገባ ተግባራዊ ተደርጓል፣

👉 በመርሐግብሩ ከ600 በላይ ለሚሆኑ የተማሪ ወላጆች የስራ ዕድል ተፈጥሯል፣

👉 ለልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ትኩረት በመስጠት 3ሺ 989 ልዩ ድጋፍ የሚሹ ተማሪዎች ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፣

👉 በ78 ማስተባበሪያ ጣቢያዎች ከ 2ሺ 600 በላይ ጎልማሶች የቀለም ትምህርት እንዲከታተሉ ተደርጓል፣

👉 የመማሪያ መፅሀፍ ስርጭት ምጣኔን በዋና ዋና ትምህርቶች 1 መፅሀፍ ለአንድ ተማሪ ማድረስ ተችሏል፣

👉 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት የትምህርት ተደራሽነትን ማረጋገጥ ተችሏል፣

👉 አዳዲስ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክቶቸ ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል፣

👉 ከአንድ ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ዳር መብራቶች ተጠግነው ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን ገልጸዋል።

👉 ባለፉት 6 ወራት በመንገድ ዳር ግብይት የሚፈጽሙ 2 ሺህ 261 ህገወጥ ነጋዴዎች ላይ ርምጃ ተወስዷል

👉 በከተማው በህገወጥ መንገድ ተወሮ የነበረ 2 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት ወደ መንግስት እንዲመለስ ተደርጓል፣

የካቲት 19 ቀን 2017 ዓም

Scroll to Top