የክልል ምክር ቤቱ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልል ሴክተር መስሪያ ቤቶችን የኦዲት ግኝቶችን በመገምገም ላይ ይገኛል።

የክልል ምክር ቤቱ የበጀት እና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ የ2012-2015 የክልል ሴክተር መስሪያ ቤቶች የኦዲት ግኝቶችን እየተመለከተ ሲሆን በዚሁ መሰረትም በዛሬው ዕለት ቋሚ ኮሚቴው የክልሉን ፕላን ኮሚሽን፣ የህብረት ስራ ኤጀንሲ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ፣ የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽንን የ2012-2015 የኦዲት ግኝቶችን ገምግሟል።

በኦዲት ግኝቱ ላይ የየተቋማቱ/መ/ቤቶቹ ኃላፊዎችና የግዥና ፋይናንስ ዳይሬክተሮቻቸው በኦዲት ግኝቱ ዙርያ ከክልል ምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራርያ ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የሐረሪ ክልል ምክር ቤት በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ፋቲሃ ሳኒ ግኝት የተገኘባቸው ተቋማትና ሴክተር መስሪያ ቤቶቹ በ15 ቀናት ውስጥ በግኘቶቻቸው ላይ ትኩረት በማድረግ ግኝቶቻቸውን አስተካክለው ሪፖርት ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

************

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት

የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት/

➥ ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/hararicouncil/

➥ ቴሌግራም:▸ https://t.me/hararicouncil_info

➥ ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/channel/

➥ ትዊተር፦ https://twitter.com/hararicouncil

➥ ፍለከሪ፡-https://www.flickr.com/photos/harari people regional council/

➥ ድረገጽ፦http://www.hararicouncil.gov.et/

አብራችሁን ስለሆናችሁ ደስተኞች ነን.

All reactions:

Scroll to Top