የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ከሐረሪ ክልል ምክር ቤት የጋራ ልምድ ልውውጥ አደረገ።
*******
የልምድ ልውውጡ የምክር ቤቶቹን ግንኙነት በማጠናከር ህዝብን በፍታሀዊነት ለማገልገል ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገልጿል ።
የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና የስራ አመራሮች ከሐረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና የስራ አመራሮች ጋር የልምድ ልውውጥ አድርጓል።
የሐረሪ ክልል ምክርቤት ም/አፈጉባኤ አቶ ሀሪፊ መሀመድ በበኩላቸው ስለ ሀረሪ ክልል ምክር ቤት አመሰራርት እና የአሰራር ስርአት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ምክርቤቶች በህገመንግስቱ የተሰጠውን ስልጣን በአግባቡ በመጠቀም ህዝብን በታማኝነት ለማገልገል በጋራ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
ልምድ ልውውጡ ለሁለቱም ክልል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልፀው በተለይም አጎራባች የክልል ምክርቤቶች የጋራ መድረክ በማዘጋጀት ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልፀዋል ።
************
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት
የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት/
➥ ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/hararicouncil/
➥ ቴሌግራም:▸ https://t.me/hararicouncil_info
➥ ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/channel/
➥ ትዊተር፦ https://twitter.com/hararicouncil
➥ ፍለከሪ፡-https://www.flickr.com/photos/harari people regional council/
➥ ድረገጽ፦http://www.hararicouncil.gov.et/
አብራችሁን ስለሆናችሁ ደስተኞች ነን.





All reactions: