የምክር ቤቱ ጽ/ቤት

አቶ ገዛኸኝ በቀለ

የምክር ቤት ጽ/ቤት ሀላፊ

የጽህፈት ቤቱ ስልጣንና ተግባር

ጽህፈት ቤቱ የሚከተሉት ስልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፡-

፩. ለምክር ቤቱና ምክር ቤቱ ለሚያቋቁማቸው ኮሚቴዎችና አደረጃጀቶች አጠቃላይ ሙያዊ ድጋፍና አስተዳደራዊ አገልግሎት ይሰጣል፤

፪. በምክር ቤቱ አባላት እና አካላት ለሚከናወኑ የህግ ማውጣት፣ የክትትልና ቁጥጥር እና የህዝብ ውክልና ስራዎች ሙያዊ ድጋፍ ይሰጣል፤

፫. በአስተዳደሩ በየደረጃው የሚገኙ የህዝብ ምክር ቤቶች የማስፈጸም አቅም የሚጠናከርበትን ስልት በማውጣት ስራ ላይ ያውላል፤

፬. ለምክር ቤቱ ጠቅላላጉባኤና ልዩ ልዩ ኮሚቴዎች የሚያስፈልጉትን የመሰብሰቢያ አዳራሾች ያደራጃል፤

፭. የምክር ቤቱን ቃለ-ጉባኤዎች፣ ውሳኔዎችና ሰነዶች በሚገባ ተመዝግበው እንዲጠበቁ ያደርጋል፡፡

፮.ለምክር ቤቱ አባላትና አካላት የቤተ-መጻሀፍት፣ የምርምርና የመረጃ አገልግሎት ይሰጣል፤

፯. ምክር ቤቱ ያጸደቃቸውን ህጎች በድሬ ነጋሪት ጋዜጣ እንዲታተሙ ያደርጋል፤ የምክር ቤቱን መጽሔቶችና ጋዜጦች ህትመትና ስርጭት ይከታተላል፤

፰. አፈ-ጉባዔው በሚሰጠው አመራር መሰረት ለምክር ቤቱ እንግዶች አስፈላጊውን የመስተንግዶ አገልግሎት እንዲያገኙ ያደርጋል፤

፱. ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከር ፀጥታና ደህንነት መከበሩን ይከታተላል፣ በማንኛውም የምክር ቤቱ ቅጥር ግቢ ፀጥታና ሥነ-ሥርዓት መከበ

ሩን ያረጋግጣል፤

፲. ለምክር ቤቱ አባላት እና አካላት በህግ የተወሰኑ ጥቅማ ጥቅሞችን እና ልዩ መብቶችን ያስፈጽማል፡፡

፲፩. በተለያዩ የሙያ ዘርፎችና ጉዳዮች ላይ ለምክር ቤቱ እና ለአካላቱ የማማከር አገልግሎት ይሰጣል፣ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ይሰራል፤

፲፪. የምክር ቤቱን ስራዎችና የምክር ቤቱን ስልጣን እና ተግባር የሚመለከቱ ጉዳዮችን በተመለከተ ዜናዎችንና መዋእለ ዜናዎችን ያሰባስባል፤ ያዘጋጃል፤ የተለያዩ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን በድረ-ገጽና በልዩ ልዩ ዘዴዎች ያሰራጫል፤

፲፫. የአቅም ግንባታ ስራዎችን ይሰራል፤

፲፬. የንብረት ባለቤት ይሆናል፤ ውል ይዋዋላል በስሙ ይከሳል ይከሰሳል፤

፲፭ የምክር ቤቱን አካላትና አባላት ሥራ ለማሳካት የሚረዱ እና በአፈ-ጉባኤው የሚሰጡ ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል፡፡

Scroll to Top